Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በትግራይ ክልል እየተከናወነ ስላለው የሰብዓዊ እንቅስቃሴ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ገለፃ ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ በትግራይ ክልል እየተከናወነ ስላለው የሰብዓዊ እንቅስቃሴ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ገለፃ አድርገዋል፡፡
ገለፃው የምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ስርጭትን ጨምሮ ሰብዐዊ እንቅስቃሴዎችን ለመፍታት ያለመ ሲሆን÷ በትብብር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይም ተወያይተዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች ተወካዮች እና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች መገኘታቸውን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version