Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ እና የኬንያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመተባበር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና የኬንያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሰላምና ልማት ዙሪያ ለመተባበር ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለፀ።
በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ የተመራ ልዑክ ከኬንያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሊቀመንበር ቢሾብ ጆሰፍ ማታው ጋር ባደረጉት ውይይት በሰላምና ልማት ዙሪያ ለመተባበር ስምምነት ላይ መድረሳቸው ችለዋል፡፡
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ልዑካን ቡድን በናይሮቢ የሚገኙ የኢትዮጵያውያን የእምነት ተቋማት ተወካዮች ጋር ዛሬ በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውይይት ማድረጋቸው ተጠቁመዋል።
በናይሮቢ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ቅርንጫፍ ለመመስረት አደራጅ ኮሚቴ መሰየሙን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version