አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 30 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሁሉም ክልሎች በ4 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ወጪ መሰረታዊ ሸቀጦች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ መደረጉን የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴሩ የዋጋ ውድነቱን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን በተመለከተ እንደገለፀው÷ መንግስት በድጎማ የሚያቀርባቸውን መሰረታዊ ሸቀጦች ከራሱ ምንጭ የውጭ ምንዛሬ በመመደብና የውጭ ምንዛሬ ባላቸው ባለሃብቶች ከታክስና ከግብር ነጻ ሆኖ ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገባ እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም ዘይት፣ ስንዴ፣ ሩዝ፣ የህጻናት የዱቄት ወተት አቅርቦት በሃገር ውስጥ ያሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ሰብል አምራች አርሶ አደሮች፣ የሸማቾች የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖችን በማስተሳሰር በሁሉም ክልሎች 14 ሚሊየን ኩንታል በመግዛት በተመጣጣኝ ዋጋ ምርታቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጓል።
ይህም በብር ሲተመን 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር መሆኑን ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

