Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በመዲናዋ በአንድ ወር የግብር መክፈያ ወቅት ከ5 ነጥብ 8 ቢሊየን በላይ ብር ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ከሀምሌ 01 እስከ ሀምሌ 30/2013 ዓ.ም በሶስቱም ደረጃ ግብር ከፋዮች 5 ቢሊየን 820 ሚሊየን 260 ሺህ ብር መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡

ቢሮው ለመሰብሰብ ካቀደው 5 ቢሊየን 390 ሚሊየን 930 ሺህ ብር የሰበሰበው 5 ቢሊየን 820 ሚሊየን 260 ሺህ ብር ነው፡፡

በዚህም የዕቅዱን 108 በመቶ ማሳካት መቻሉ ነው የተገለፀው፡፡

ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 1 ቢሊየን 126 ሚሊየን 950 ሺህ ብር ወይም 24 በመቶ ብልጫ መኖሩ የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ተፈራ መግለጻቸውን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version