Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የሀረሪ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሰራተኞች ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀረሪ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አመራርና ሰራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የአንድ ወር ደመወዛቸውን ድጋፍ አድርገዋል፡፡

የቢሮው አመራርና ሰራተኞች በዛሬው ዕለት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡

በዚህም ሀገርን ለማዳን ተጋድሎ እያደረገ ለሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የክልል የጸጥታ አካላት የአንድ ወር ደሞዛቸውን ለመለገስ ቃል ገብተዋል።

የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ሲያደርጉ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን ከሀረሪ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version