አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደሴ ከተማ የሚኖሩ የተለያየ ማሕረሰብ ተወካዮች ግንባር ድረስ በመሄድ የስንቅ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ለሠራዊቱ ያላቸውን ደጀንነት ለማሳየት በተወካዮቻቸው አማካኝነት በግንባር በመገኘት ባስረከቡበት ወቅት÷ አረመኔው የሽብር ቡድን እስከሚደመሰስ ድረስ ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የመከላከያ ሰራዊት አመራር አባላት በበኩላቸው÷ የደሴ ከተማ ህዝብ ደጀንነቱን ለማስመስከር ያደረገውን ድጋፍ አድንቀው÷ ድጋፉም ከድጋፍነት የተሻገረ ትርጉም ያለው እንደሆነና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
ይኸው ድጋፍም አሸባሪውን የህወሓት ቡድን በመደምሰስ ሂደት ከፍተኛ የሞራል ስንቅ እንደሚሆናቸው ነው የተናገሩት፡፡
ድጋፉን ለማድረስ ግንባር ድረስ የተገኙ የከተማዋ ነዋሪ ተወካዮችም÷ ከምንም በላይ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለሀገር ህልውና እየከፈለ ያለውን ዋጋ መመልከታቸውን ገልፀዋል፡፡
በሐብታሙ ተክለሥላሴ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

