Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በድንጋይ ያባረርነው አሸባሪው ህወሓት እኛ እያለን ሀገራችንን አያፈርስም – የአርሲ ዞን ወጣቶች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በድንጋይ ያባረርነው አሸባሪው ህወሓት እኛ እያለን ዳግም የኦሮሚያን መሬት አይረግጥም፤ ሀገራችንንም አያፈርስም ሲሉ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን የተቀላቀሉ የአርሲ ዞን እና የአሰላ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ።

የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ለተቀላቀሉ የአርሲ ዞን እና የአሰላ ከተማ ወጣቶች የጀግና ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

እንደ ኦቢኤን ዘገባ ወጣቶቹ በፈቃዳቸው መከላከያን ለመቀላቀል የወሰኑት ሀገርን ለማፍረስ የሚንፈራገጡትን ኃይሎች በአጭር ጊዜ ወደ ቦታቸው ለመመለስ መሆኑን ተናግረዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version