አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ /ኢዜማ/ በአሸባሪው ህወሓት ወረራ ከቀያቸው ተፈናቅለው ደሴ ከተማ ለሚገኙ ዜጎች ከ1 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ አልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውለውን ድጋፍ የኢዜማ አመራርና አባላት በደሴ ትግል ፍሬ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለተጠለሉ ዜጎች እንዲውል አስረክበዋል።
የኢዜማ የሴቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ቅድስት ግርማይ በአሸባሪው የህወሓት ወራሪ ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መደገፍ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት መሆኑን መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

