አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)ጨፌ ኦሮሚያ አቶ ገዛሊ አባሲመልን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ፣አቶ ጉዮ ዋሪዮን ደግሞ ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ ሾሟል።
በሌላ በኩል አቶ ተፈሪ ወንዳፈራሁ የክልሉ ዋና ኦዲተር እና አቶ ቶለሳ አቦማ ምክትል ኦዲተር አድርጎ ሾሟል።
በተጨማሪም ጨፌው አቶ ሁሴን ኡስማንን የክልሉ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርጎ በመሾም ጉባኤውን ማጠናቀቁን ከኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!