Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ በቡድኖች ፍላጎት አትፈርስም – የሰመራ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት የምትፈርስ ሀገር አይደለችም ሲሉ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ አሸባሪው ህወሓት በየአከባቢው በንፁሃን ላይ እያደረሰ ያለውን ግድያና ዝርፊያ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ነዋሪዎች ገለጹ።
ሰልፈኞቹ አሸባሪው ህወሓት በንፁሀን ላይ እያደረሰ ያለው ጭፍጨፋን በመቃወም እያካሄዱት ባለው ሰልፍ አለም አቀፉ ማህበረሰብ የአሸባሪውን እኩይ ተግባር እንዲገነዘብ ጠይቀዋል።
በሰልፉም÷ እኛ አፋሮች እያለን ኢትዮጵያ መቼም ቢሆን አትደፈርም፣ በሉዓላዊነታችን ውስጥ ማንም ጣልቃ እንዲገባ አንፈቅድም የሚሉ መልዕክቶች ተላልፈዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version