አዲስ አበባ፣ ህዳር 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሊቢያ አዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እንደዘጋጅ ተደርጎ እየተሰራጨ ያለውን ሀሰተኛ መረጃ አስተባበለች፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ ኤምባሲው ስራ ላይ መሆኑን እና የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡
አንዳንድ የአፍሪካ አገራት የአዲስ አበባ ኤምባሲዎቻቸውን መዝጋታቸውን እና ሊዘጉ ዝግጅት እያደረጉ እንደሆነ ተደርጎ የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ በመንግስት ላይ እየተካሄደ ያለው የውጭ ጫና እና የሥነ ልቦና ጦርነት አካል መሆኑን አምባሳደር ዲና ተናግረዋል፡፡
ሌሎች የተያያዙ መረጃዎች ተጣርተው ለህዝብ ይፋ እንደሚደረጉም ቃል አቀባዩ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

