አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ልዩ መልእክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ አዲስ አበባ መግባታቸውን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።
ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በመገናኘት ፣ የሰላም መፍትሔ በማፈላለግ ሂደታቸው የደረሱበትን ሐሳብ እንደሚያብራሩ ነው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የገለጸው።
በተጨማሪም በሰብአዊ ርዳታ ዙሪያ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።
ኦባሳንጆ በዚሁ ቆይታቸው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የአፍሪካ ኅብረት አምባሳደሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ እስካሁን በደረሱባቸው ነጥቦች ዙሪያ ማብራሪያ እንደሚሰጡ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

