Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኢትዮጵያ በ24 ሰዓት ውስጥ 5 ሺህ 13 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በኢትዮጵያ በ24 ሰዓት ውስጥ 5 ሺህ 13 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ባወጣው ዕለታዊ መረጃ በ24 ሰዓት ውስጥ 14 ሺህ 27 የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሺህ 13 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አስታውቋል፡፡

እንዲሁም 6 ሰዎች በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡

በአንፃሩ 106 ሰዎች ከቫይረሱ ማገገም ችለዋል፡፡

በኢትዮጵያ እስከአሁን ለ4 ሚሊየን 41 ሺህ 996 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል፡፡

Exit mobile version