አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶጊዳ ወረዳ ጋሪ ቀበሌ ለአሸባሪው ሸኔ ለማቀበል ሲጓጉዙ የነበረ 1 ሺህ 103 ጥይት በቁጥጥር ስር መዋሉን የወረዳው ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ገልጿል፡፡
የተያዙት 518 የብሬን እና 585 የክላሽ ጥይቶች በድምሩ 1 ሺህ 103 ጥይቶች መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል።
ጥይቶቹ የተያዙት በህዝብ ጥቆማና በጸጥታ አካላት ትብብር መሆኑም የወረዳው ፖሊስ ገልጿል፡፡
የወረዳው ፖሊስ ሃላፊ ዋና ሳጅን ከተማ ኦልጅራ እንደገለጹት÷ ጥይቱ ትናንት ከምሽቱ 3 ሠዓት ላይ ከነቀምቴ ከተማ ወደ ወላኔ ተራራ ለአሸባሪው ሸኔ ሊጓጓዙ ነው የተያዙት፡፡
በገላና ተስፋ
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

