Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ የተመራ ቡድን በሶማሌ ያለውን የድርቅ ሁኔታ ለመመልከት ጎዴ ገባ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ የተመራ ቡድን በሶማሌ ክልል ያለውን የድርቅ ሁኔታ ለመመልከት ጎዴ ገብቷል፡፡

ቡድኑ በሸበሌ ዞን በሚኖረው ቆይታ÷ በድርቅ ምክንያት ከብቶቻቸውን ያጡ አርብቶ አደር ቤተሰቦች እስካሁን እየተደረገላቸው ያለውን የእርዳታና ድጋፍ ሁኔታ እንደሚመለከት ተገልጿል።

አርብቶ አደሮቹን በዘላቂነት ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከክልሉ የስራ ኃላፊዎች ጋር ቡድኑ እንደሚወያይ ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Exit mobile version