Fana: At a Speed of Life!

በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ የተመራ ቡድን በሶማሌ ያለውን የድርቅ ሁኔታ ለመመልከት ጎዴ ገባ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ የተመራ ቡድን በሶማሌ ክልል ያለውን የድርቅ ሁኔታ ለመመልከት ጎዴ ገብቷል፡፡

ቡድኑ በሸበሌ ዞን በሚኖረው ቆይታ÷ በድርቅ ምክንያት ከብቶቻቸውን ያጡ አርብቶ አደር ቤተሰቦች እስካሁን እየተደረገላቸው ያለውን የእርዳታና ድጋፍ ሁኔታ እንደሚመለከት ተገልጿል።

አርብቶ አደሮቹን በዘላቂነት ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከክልሉ የስራ ኃላፊዎች ጋር ቡድኑ እንደሚወያይ ኢዜአ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.