አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል ፖሊስ “ዛሬም እንደ ትናንቱ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን፣ እጃችንን ለምስጋና እንዘረጋለን”ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባስተላለፉት መልዕክት መሰረት የምስጋና መርሐ ግብር አከናውኗል።
በመርሐ ግብሩ የፌዴራል ፖሊስ ሠራዊት ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል፣ የፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ሠራተኞች ተገኝተዋል።
ሁሉም ቀኝ እጃቸውን ግራ ደረታቸው ላይ በማድረግ ለአንድ ደቂቃ በመቆም አመስግነዋል።
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!