Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በወልዲያ ከተማ በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው የአስተዳደር ሕንጻ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በወልዲያ ከተማ የተገነባውን ባለ 6 ወለል የከተማ አስተዳደር ሕንጻ መረቁ፡፡
ለግንባታው 138 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገ ሲሆን ገንዘቡም በከተማ አስተዳደሩ መሸፈኑ ተመላክቷል፡፡
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተገለጸው÷ ወልዲያ ከተማ ወደ ሪጂኦፖሊታንት ከተማ ማደጓን ተከትሎ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመሥጠት እንዲቻል መሰል ፕሮጀክቶች ያስፈልጋሉ፡፡
የወልዲያ ከተማ አሁን ካለችበት ከፈርአንድ ወደ ሪጂዮፖሊታንት ደረጃ ሽግግር ስነ ስርዓት እየተካሄደ ነው፡፡
በታሪኩ ለገሰ
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version