Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የ11 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በጽህፈት ቤታቸው በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የ11 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ።

አምባሳደሮቸ የኢራን ፣ ቤልጂየም ፣ ኖርዌይ ፣ ኒጀር ፣ ኦስትሪያ ፣ ብራዚል፣ ኩዌት ፣ ሳኡዲ አረቢያ ፣ ፓርቹጋል ፣ ሲንጋፓር እና ዶሚኒካን ሪፐብሊክ ናቸው።

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ የሹመት ደብዳቤ ካቀረቡ አምባሳደሮች ጋር በኢትዮጵያ እና በሀገራቱ መካከል ያሉ ግንኙነቶችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version