Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮንትሮባንድ ንግድን በቅንጅት ለመቆጣጠር እየመከረ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮንትሮባንድ ንግድን በቅንጅት ለመቆጣጠር ከፀጥታ ኃይሎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው፡፡

በውይይት መድረኩ በክልሉ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ የኮንትሮ ባንድ ንግድ በዘላቂነት መከላከልና በተቀናጀ አግባብ መቆጣጠር የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ እንደሚያዝ ይጠበቃል፡፡

በመድረኩ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሐሰንን ጨምሮ የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ ፣ የተለያዩ የክልልና የፌዴራል ፀጥታ ዘርፍ ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት መገኘታቸውን የክልሉ ርዕሠ-መስተዳድር ፅኅፈት ቤት መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version