Fana: At a Speed of Life!

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮንትሮባንድ ንግድን በቅንጅት ለመቆጣጠር እየመከረ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮንትሮባንድ ንግድን በቅንጅት ለመቆጣጠር ከፀጥታ ኃይሎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው፡፡

በውይይት መድረኩ በክልሉ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ የኮንትሮ ባንድ ንግድ በዘላቂነት መከላከልና በተቀናጀ አግባብ መቆጣጠር የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ እንደሚያዝ ይጠበቃል፡፡

በመድረኩ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሐሰንን ጨምሮ የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ ፣ የተለያዩ የክልልና የፌዴራል ፀጥታ ዘርፍ ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት መገኘታቸውን የክልሉ ርዕሠ-መስተዳድር ፅኅፈት ቤት መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.