Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመሪያ የቻይና በረራውን የካቲት 14 ቀን 1965 ዓ.ም ወደ ሻንጋይ ከተማ በማድረግ አገልግሎቱን መጀመሩን አስታውሷል፡፡

ከጥቅምት 28 ቀን 1966 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ መዳረሻውን ወደ ቤጂንግ ከተማ በመቀየር አገልግሎን መቀጠሉንም የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በ5 የመንገደኛ እና በ9 የዕቃ ጭነት መደበኛ በረራዎች አገልግሎት እየሠጠ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ 66 ሳምንታዊ በረራዎችን ወደ 10 የቻይና ከተሞች እንደሚያደርግም አስታውቋል፡፡

መዳረሻዎቹም ቤጂንግ፣ ጓንዡ፣ ሼንጁ፣ሻንጋይ፣ ሸንዘን ፣ ውሀን፣ ቻንግሻ፣ ዢያመን፣ ቸንዱ እና ሆንግ ኮንግ መሆናቸውንም አየር መንገዱ ጠቁሟል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version