Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ በሀገራቱ የድንበር አዋሳኝና ከቀጠናው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ አንፃር አብረው መስራት በሚገባቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረው መግባባት ላይ መድረሳቸውን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡

የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Exit mobile version