Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ለ3ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጎዳና ላይ ኢፍጣር የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን ለ3ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

የጎዳና ላይ ኢፍጣሩ “ኢፍጣራችን ለወገናችን” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደሚካሄድም ተጠቁሟል፡፡

ረመዳን የአብሮነት ፣ የመረዳዳት እንዲሁም የዕዝነት ወር እንደመሆኑ በዕለቱ ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ ይሰባሰባል ተብሏል።

በአፍጥር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ህዝበ ሙስሊሙ ለአፍጥር በቤት ያዘጋጀውን ይዞ በመገኘት የወንድማማችነት ግንኙነቱን እንዲያጠናክር ጥሪ ቀርቧል።

ሥነ-ሥርዓቱን የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከነጃሺ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ይመራዋል።

መርሐ-ግብሩ የተሳካ እንዲሆን በዕለቱ ከ4 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

በፈቲያ አብደላ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version