በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ለ3ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጎዳና ላይ ኢፍጣር የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን ለ3ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
የጎዳና ላይ ኢፍጣሩ “ኢፍጣራችን ለወገናችን” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደሚካሄድም ተጠቁሟል፡፡
ረመዳን የአብሮነት ፣ የመረዳዳት እንዲሁም የዕዝነት ወር እንደመሆኑ በዕለቱ ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ ይሰባሰባል ተብሏል።
በአፍጥር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ህዝበ ሙስሊሙ ለአፍጥር በቤት ያዘጋጀውን ይዞ በመገኘት የወንድማማችነት ግንኙነቱን እንዲያጠናክር ጥሪ ቀርቧል።
ሥነ-ሥርዓቱን የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከነጃሺ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ይመራዋል።
መርሐ-ግብሩ የተሳካ እንዲሆን በዕለቱ ከ4 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
በፈቲያ አብደላ