አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አዲሱ “የመደመር ትውልድ” መጽሐፍ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል በኦንላይን ገበያ ለሽያጭ ቀርቧል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተጻፈውና በቅርቡ የተመረቀው “የመደመር ትውልድ” መጽሐፍ በተለያዩ አካባቢዎች ለገበያ መቅረቡ ይታወቃል፡፡
አሁን ላይም “የመደመር ትውልድ” መጽሐፍ በኢትዮ ፖስት(Ethio Post shop) በኩል በኦንላይን ገበያ ለሽያጭ ቀርቧል፡፡
ስለሆነም በቀጣዩ ሊንክ በመግባት ethio.post/product/genera በዓለም አቀፍ እና በመደበኛ የመገበያያ ዘዴዎች ክፍያ በመፈጸም መጽሐፉን መግዛት እንደሚቻል ተገልጿል፡፡

