Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አምባሳደር ተፈራ ደርበው ከቻይና የአፍሪካ ልማት ፈንድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ከቻይና የአፍሪካ ልማት ፈንድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሺ ዌንጁ ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸው አምባሳደር ተፈራ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የኢንቨስትመንት ፎረም እና በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች ዙሪያ መክረዋል።

የአፍሪካ ልማት ፈንድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሺ ዌንጁ የቻይና የአፍሪካ ልማት ፈንድ በአፍሪካ ኢንቨስት በማድረግ እና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ ረገድ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የቻይና ልማት ፈንድ በመጭው ሰኔ ወር በሚዘጋጀው የቻይና -አፍሪካ የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ሲምፖዚየም ላይ አምባሳደር ተፈራን ጨምሮ የኤምባሲው ሰራተኞች እንዲሳተፉ ጋብዘዋል፡፡

Exit mobile version