አምባሳደር ተፈራ ደርበው ከቻይና የአፍሪካ ልማት ፈንድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ከቻይና የአፍሪካ ልማት ፈንድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሺ ዌንጁ ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይታቸው አምባሳደር ተፈራ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የኢንቨስትመንት ፎረም እና በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች ዙሪያ መክረዋል።
የአፍሪካ ልማት ፈንድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሺ ዌንጁ የቻይና የአፍሪካ ልማት ፈንድ በአፍሪካ ኢንቨስት በማድረግ እና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ ረገድ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የቻይና ልማት ፈንድ በመጭው ሰኔ ወር በሚዘጋጀው የቻይና -አፍሪካ የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ሲምፖዚየም ላይ አምባሳደር ተፈራን ጨምሮ የኤምባሲው ሰራተኞች እንዲሳተፉ ጋብዘዋል፡፡