Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሩሲያ በባክሙት የዩክሬን ወታደሮች ተቆርጠው መቅረታቸውን አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በባክሙት ከተማ የዩክሬን ወታደሮች ተቆርጠው መቅረታቸውን አስታውቃለች፡፡

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ በባክሙት ተቆርጠው የቀሩት የዩክሬን ወታደሮች በሩሲያ ሃይሎች ከበባ ውስጥ መግባታቸውን አረጋግጧል፡፡

የሩሲያ አየር ወለድ የተቆረጡት የዩክሬን ወታደሮች ምንም አይነት መውጫ እና ድጋፍ እንዳያገኙ አስፈላጊውን ሁሉ እያደረገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ዩክሬን በበኩሏ÷ ወታደሮቿ ተቆርጠዋል የሚለውን መረጃ ውድቅ በማድረግ በስፍራው ከሚገኙት ወታደሮች ጋር እስካሁን ግንኙነት መኖሩን አስታውቃለች፡፡

የዩክሬን ወታደሮች በባክሙትን መልሶ ለመቆጣጠር የተጠናከረ ዘመቻ መክፈታቸውንም አልጀዚራ በዘገባው አስፍሯል፡፡

Exit mobile version