አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 6 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ተከበረ።
በዓሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፣ በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እና በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት፥ በስግደት፣ በጾም፣ በጸሎት እና በዝማሬ ነው የተከበረው፡፡
በዕለቱ ቀኑን የሚያወሱ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚነበቡ ሲሆን፥ በዕለተ ስቅለት የተከናወኑ ተግባራት እየታሰበም ይሰገዳል።

