Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጽሑፍ ሥራዎች የሚያሳይና የሚዳስስ የመጽሐፍ ዐውደ ርእይ ዛሬ በአብርሆት ይከፈታል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጽሑፍ ሥራዎች የሚያሳይ እና የሚዳስስ የመጽሐፍ ዐውደ ርእይ በአብርሆት ቤተ መዛግብት መዘጋጀቱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተዘጋጁ ህትመቶችን እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጽሁፍ ስራዎችን የሚያሳይ እና የሚዳስሰው ይህ አውደ ርዕይ ከሚያዚያ 24 እስከ ሚያዚያ 29 ቀን 2015 ለአንድ ሳምንት እንደሚቆይ ነው ጽህፈት ቤቱ ያመለከተው።

በእነዚህ ቀናትም ዜጎች በአብርሆት ቤተ መዛግብት መተው እንዲካፈሉ ጽህፈት ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

Exit mobile version