Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኅብረቱ አሥቸኳይ የተኩስ አቁም ጥሪ ለሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች አቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ኅብረት አሥቸኳይ የተኩስ አቁም ጥሪ ለሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች አቀረበ፡፡

ኅብረቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ ሱዳናውያን የውሃ፣ የጤና እና የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች መሰረታዊ ግብዓቶችን እንዲያገኙ ተፋላሚ ኃይሎች በአስቸኳይ ጦርነቱን አቁመው እንዲወያዩ አሳስቧል፡፡

ኅብረቱ ከተኩስ አቁም ጎን ለጎንም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሱዳናውያን ሰብዓዊ አቅርቦት እና የተቀናጀ ድጋፍ እንዲያደርስም ጠይቋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ለጉዳዩ ዕልባት ለመሥጠት በፈረንጆቹ ባሳለፍነው ሚያዚያ 20 ላይ ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ስብሰባ መጥራቱ ይታወሳል፡፡

በአፍሪካ ኅብረትና በተመድ የሚመራ ቡድን በሱዳን ፣ በቀጣናው ብሎም በአኅጉሪቱ የሚስተዋለውን ሁከትና አለመረጋጋት ለማስቆም ዓለም አቀፍ እርምጃዎችን እንደሚያስተባብርም ተጠቁሟል፡፡

የተሠጡት የውሳኔ ሐሳቦችም በአፍሪካ ኅብረት መርኅዎች የተደገፉ መሆናቸው ነው የተገለጸው፡፡

በአፈፃፀሙ ላይ ያተኮረ ስብሰባም በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ዛሬ ይካሄዳል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version