Fana: At a Speed of Life!

ኅብረቱ አሥቸኳይ የተኩስ አቁም ጥሪ ለሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች አቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ኅብረት አሥቸኳይ የተኩስ አቁም ጥሪ ለሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች አቀረበ፡፡

ኅብረቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ ሱዳናውያን የውሃ፣ የጤና እና የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች መሰረታዊ ግብዓቶችን እንዲያገኙ ተፋላሚ ኃይሎች በአስቸኳይ ጦርነቱን አቁመው እንዲወያዩ አሳስቧል፡፡

ኅብረቱ ከተኩስ አቁም ጎን ለጎንም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሱዳናውያን ሰብዓዊ አቅርቦት እና የተቀናጀ ድጋፍ እንዲያደርስም ጠይቋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ለጉዳዩ ዕልባት ለመሥጠት በፈረንጆቹ ባሳለፍነው ሚያዚያ 20 ላይ ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ስብሰባ መጥራቱ ይታወሳል፡፡

በአፍሪካ ኅብረትና በተመድ የሚመራ ቡድን በሱዳን ፣ በቀጣናው ብሎም በአኅጉሪቱ የሚስተዋለውን ሁከትና አለመረጋጋት ለማስቆም ዓለም አቀፍ እርምጃዎችን እንደሚያስተባብርም ተጠቁሟል፡፡

የተሠጡት የውሳኔ ሐሳቦችም በአፍሪካ ኅብረት መርኅዎች የተደገፉ መሆናቸው ነው የተገለጸው፡፡

በአፈፃፀሙ ላይ ያተኮረ ስብሰባም በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ዛሬ ይካሄዳል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.