Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሞስኮ በክሬሚሊን አቅራቢያ ሲበሩ ነበሩ ያለቻቸውን የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች መትታ መጣሏን ገለፀች

A still image taken from video shows a flying object exploding in an intense burst of light near the dome of the Kremlin Senate building during the alleged Ukrainian drone attack in Moscow, Russia, in this image taken from video obtained by Reuters May 3, 2023. Ostorozhno Novosti/Handout via REUTERS

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሞስኮ ክሬሚሊን በሚገኘው የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቤተ መንግሥት አቅራቢያ ሲበሩ ነበሩ ያለቻቸውን የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች መትታ መጣሏን ገለፀች።

በክሬምሊን አቅራቢያ ትናንት ምሽት ሲበሩነበሩ የተባሉት ሁለቱ ሰው አልባ አውሮፕላኖች በፕሬዚዳንት ፑቲን ላይ ጥቃት ለማድረስ ነበር ተብሏል፡፡

የፕሬዚዳንት ፑቲን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለሀገሪቱ የዜና ምንጭ እንደተናገሩት ÷ በወቅቱ ፕሬዚዳንቱ በቤተ መንግሥታቸው አልነበሩም፡፡

በሕንጻዎቹ ላይም የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት አለመኖሩንም ተናግረዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ሞስኮ ሰው አልባ አውሮፕላኖቹን ልዩ የኤሌክትሮኒክ ራዳር ሞገድ በመጠቀም መጣሏንም ነው ያስታወቀችው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version