Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

82ኛው የዐርበኞች የድል መታሰቢያ በዓል እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 82ኛው የዐርበኞች የድል መታሰቢያ በዓል እየተከበረ ነው።
 
በዓሉ አራት ኪሎ በሚገኘው የዐርበኞች ሃውልት ዙሪያ ነው በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ የሚገኘው ።
 
በአከባበር ሥነ-ሥርዓቱ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች ዐርበኞች ማህበር አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
 
በዓሉን ምክንያት በማድረግም ንጋት ላይ መድፍ ተተኩሷል።
 
በመሳፍንት እያዩ
Exit mobile version