Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር  ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ  ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክረናል ብለዋል።

በኢትዮጵያ እና በብራዚል መካከል ግንኙነትን ስለማጠናከር እና በብዝኃ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት እናደርጋለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡

Exit mobile version