Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሐረር ከተማ ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 444ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሐረር ከተማ ተከብሯል፡፡

በዓሉ በርካታ የእስልምና እምነትተከታዮች በተገኙበት ሰላት እና ተክቢራን ጨምሮ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶች ነው የተከበረው፡፡

በሐረር ከተማ በተካሄደው የሰላት ስነ-ስርዓት ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያለው ህዝበ ሙስሊም ተገኝቷል፡፡

የሐረር ጁምዐ መስጅድ ኢማም ሼክ ሙክታር ሙባሪክ ÷ በዓሉ የመስዋዕትነትና የመታዘዝ በመሆኑ ለፈጣሪ መገዛት እንደሚያስፈልግ እና ለሠላምና አንድነት ህዝበ ሙስሊሙ መትጋት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።

ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብርም በመተጋገዝና በመደጋገፍ ሊሆን እንደሚገባ ሼክ ሙክታር አሳስበዋል።

በተሾመ ኃይሉና ቱጂ አብዲ

Exit mobile version