Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ዒድ አል አድሃ በዓል በደሴ እና ወልዲያ ከተሞች ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 444ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በደሴ እና ወልዲያ ከተሞች ተከብሯል፡፡

በዓሉ በርካታ የእስልምና እምነትተከታዮች በተገኙበት ነው በሶላት ስነ-ስርዓት የተከበረው፡፡

በስነ-ስርዓቱ ላይ ተክቢራን ጨምሮ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶችም ተከናውነዋል፡፡

የደሴ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ÷ በደሴ ከተማ የአረፋ ሰላት በሚሰግድበት ፉርቃን መስጅድ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አቶ ሳሙኤል በመልዕክታቸው÷ ሙስሊሙ ማህበረሰቡ በዓሉን በመረዳዳትና በመተጋገዝ ሊያሳልፍ ይገባል ብለዋል።

ህዝበ ሙስሊሙ ከሚጠይቃቸው ጥያቄዎች መካከል የመስገጃ ቦታ እጥረት አንዱ መሆኑን ገልጸው÷ ችግሩን ለመፍታት ይሰራል ብለዋል።

በተመሳሳይ የዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓል በባህርዳር፣ በደብረ ብርሃን እና ሞጣ ከተሞች በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶች ተከብሯል፡፡

በከድር መሀመድ

Exit mobile version