አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢሲ) በአንድ ጀምበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ችግኝ የመትከል መርሐ-ግብሩ ማለዳ ነው መካሄድ የጀመረው፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በመርሐ-ግብሩ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
በክልሉ የተለያዩ ዞን፣ ወረዳና ቀበሌ ነዋሪዎች በመርሐ-ግብሩ ላይ በመሳተፍ አረጓንዴ አሻራቸውን በማኖር ላይ እንደሚገኙ ከክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡