አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 13 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዛሬው እለት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ለተመረቁ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈዋል፡፡
አቶ ደመቀ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባተላለፉት መልዕክት÷ በመላው ሀገራችን በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የምረቃ በዓላቸውን ላካሄዱ እንዲሁም በዝግጅት ላይ ላሉ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እፈልጋለሁ ብለዋል::
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በዛሬው እለት የምረቃ በዓሉን ማካሄዱን ያነሱት አቶ ደመቀ ÷ ተማሪዎች ለምርቃት እንዲበቁ ጥረት ላድረጉ ወላጆች እና መምህራን እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ተመራቂዎች በቀሪ ዘመናቸው ፍሬያማ ህይወት እንዲኖራቸው እና መልካም ነገር እንዲገጥማቸው መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡