Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ለተመራቂ ተማሪዎች የአንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 13 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በዛሬው እለት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ለተመረቁ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈዋል፡፡

አቶ ደመቀ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባተላለፉት መልዕክት÷ በመላው ሀገራችን በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የምረቃ በዓላቸውን ላካሄዱ እንዲሁም በዝግጅት ላይ ላሉ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እፈልጋለሁ ብለዋል::

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በዛሬው እለት የምረቃ በዓሉን ማካሄዱን ያነሱት አቶ ደመቀ ÷ ተማሪዎች ለምርቃት እንዲበቁ ጥረት ላድረጉ ወላጆች እና መምህራን እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ተመራቂዎች በቀሪ ዘመናቸው ፍሬያማ ህይወት እንዲኖራቸው እና መልካም ነገር እንዲገጥማቸው መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.