Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት በጥቃቅንና መካከለኛ ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ሴት አምራቾችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጀይ ባንጋ በሁለተኛው ቀን የኢትዮጵያ ቆይታቸው በጥቃቅንና መካከለኛ ኢንደዱስትሪ የተሰማሩ ሴት አምራቾችን ጎብኝተዋል።

በኢትዮጵያ መንግስትና የዓለም ባንክ ድጋፍ በሚንቀሳቀሰው የሴቶች ኢንተርፕሩነር ሺፕ ልማት ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶችን በማምረቻ ቦታቸው በመገኘትም አነጋግረዋል።

በጉብኝታቸው በጫማ ምርት ላይ የተሰማራውን የምስጋና ጫማ ማምረቻን የጎበኙ ሲሆን÷ በተመለከቱት ነገር እንደተደነቁ ገልፀዋል።

በርካታ ወጣት ሴቶች ባገኙት ድጋፍ ለብዙዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን በማንሳት÷ ይህን እድል ለበርካቶች መፍጠር ቢቻል ብዙ ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት እንደሚቻል ማየታቸውንም አንስተዋል።

ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ ድጋፍ ቢያገኙ ብዙ መስራት እንደሚችሉና ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን ማሳደግ ት የሚችል በርካታ የሰው ሃይል ያላት መሆኑን ማየታቸውን ፕሬዝዳንቱ ጠቅሰዋል።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version