Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አምባሳደር ሽፈራው (ዶ/ር) ከተመድ የኢትዮጵያ ተጠሪና የሰብዓዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማሪያም (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ተጠሪና የሰብዓዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ራሚዝ አላክባሮቭ (ዶ/ር) ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም በሰብዓዊ ድጋፎች ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው (ዶ/ር)÷ በኢትዮጵያ ስላለው የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ክፍተትና በኢትዮጵያ መንግስትና በተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች መካከል ስላለው ተቀራርቦ የመስራት ልምድን ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

ራሚዝ አላክባሮቭ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የስራ ቆይታ የነበረውን ተቀራርቦ የመስራት ልምድ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል፡፡

በተጨማሪም የሰብዓዊ ድጋፉን ክፍተት ለመሙላት በሚያስፈልገው ሁሉ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡

 

Exit mobile version