አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ጸጥታ ጉዳዮች ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡
በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አዋል ዋግሪስ መሐመድ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ አሕመድ ቲኑቡ አቅርበዋል።
በዚህ ወቅትም ፥ የሀገራቱ ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ መጠናከር በሚችልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አዋል ዋግሪስ ሞሐመድ ÷ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን የሁለትዮሽና የባለ-ብዙ ወገን ትብብር የበለጠ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኗንም ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው ፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!