Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በተለያዩ መሥኮች እንሰራለን አሉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ጸጥታ ጉዳዮች ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡

በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አዋል ዋግሪስ መሐመድ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ አሕመድ ቲኑቡ አቅርበዋል።

በዚህ ወቅትም ፥ የሀገራቱ ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ መጠናከር በሚችልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አዋል ዋግሪስ ሞሐመድ ÷ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን የሁለትዮሽና የባለ-ብዙ ወገን ትብብር የበለጠ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኗንም ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው ፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version