Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ከስዊድኑ “ሚልዮማንኒግ” ጋር ውል አሠረች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በክኅሎት የዳበረ እና የሠለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ስዊድን ሀገር ከሚገኘው “ሚልዮማንኒግ” ኩባንያ ጋር በትብብር መሥራት የሚያስችላትን የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመች፡፡

የክኅሎት ሥልጠናው ኢትዮጵያውያን ሕጋዊ በሆነ የአሠራር ሥርዓት ስዊዲንን ጨምሮ ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚያደርጉትን ጉዞ ከማሳለጥና አዳዲስ ክኅሎቶችን እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ የሥራ ገበያም በማዘጋጀት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ተብሏል፡፡

የሥራና ክኅሎት ሚኒስቴር ከሀገር ውስጥ ባለፈ የዓለምን የሥራ ገበያ ለመጠቀምና ፍልሰትን በአግባቡ ለማስተዳደር በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡

ሚኒስቴሩ ፍላጎቱ ያላቸውን ዜጎች በቂ ዕውቀትና ክኅሎት ይዘው እንዲሁም መብትና ደኅንነታቸው ተጠብቆ ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት ሕጋዊ በሆነ መንገድ ተሰማርተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቴክኖሎጂ የታገዘ የአሠራር ሥርዓት ዘርግቻለሁ ብሏል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version