Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የምክር ቤቱ የአቅም ግንባታ ሥራዎች አፈጻጸም አበረታች ነው – አፈ-ጉባዔ ታገሠ ጫፎ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት ቅድመ – ዝግጅት ያከናወናቸው ሥራዎችን አፈጻጸም ገምግሟል፡፡

በዚሁ ወቅት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሠ ጫፎ÷ የምክር ቤቱ ጽህፈት ቤት በቅድመ- ዝግጅት ሥራው በአቅም ግንባታ ሥራዎችና በአሰራር መመሪያዎች ማሻሻል ላይ ያለው አፈጻጸም አበረታች መሆኑን አንስተዋል፡፡

በተጨማሪም በሠራተኛ የሥራ አፈጻጸም ምዘናና በተቋሙ የውስጥ የመሰረተ-ልማት ግንባታ ማጠናቀቂያ ሥራዎች ላይ ያለው አፈፃፀም የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ቀሪ ሥራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ማሳሰባቸውንም የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

ምክር ቤቱን ማስተዋወቅ ሀገርን ማስተዋወቅ ነው ያሉት አፈ-ጉባዔው÷ በምክር ቤቱ የተጀመረው የሙዚዬም ግንባታና የቅርስ ማሰባሰብ ስራ በፍጥነት እንዲከናዎን አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

የምክር ቤቱ ም/አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በበኩላቸው÷ ለምክር ቤቱ ሙያዊና አስተዳደራዊ ድጋፍ ለሚሠጡ የጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች የተሠጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በቀጣይም የምክር ቤት አባላትን አቅም በየፈርጁ ለመገንባት የሚያስችል ዝግጅት ከወዲሁ ሊደረግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

Exit mobile version