አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የናይጄሪያ ባለሐብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ-ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ሥምምነት ላይ ተደረሰ፡፡
ባለሐብቶቹ በኢትዮጵያ ከሚገኙ አቻ ተቋማትና ባለሐብቶች ጋር ተገናኝተው እንዲሠሩ ሁኔታዎች እንደሚመቻችላቸው መገለጹን በሌጎስ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የንግድ ጉባዔ ላይ የተሳተፈው አቡጃ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል፡፡
ኤምባሲው በንግድ ጉባኤ ተሳትፎው ለኢትዮጵያ የወጪ ምርቶች ገበያ ማፈላለግ የሚያስችል ሁኔታ ማመቻቸቱን ጠቁሟል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!