Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኤስካይ 2 አዲስ ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖችን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኤስካይ (አፍሪካን ስካይ) ሁለት አዲስ ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖች መረከቡ ተገለጸ፡፡

አዲሶቹ የቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖች የነዳጅ ፍጆታ መቀነስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ያላቸው መሆናቸውንም የኤስካይ 40 በመቶ ድርሻ ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያወጣው መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላኖቹ የውስጥ ክፍል÷ ሰፊ እና ዘመናዊ ከመሆናቸው ባሻገር÷ የተሻሻሉ የመቀመጫ አማራጮች ያላቸው እንዲሁም መንገደኞች በበረራ ወቅት እየተዝናኑ እንዲጓዙ የሚያስችሉ ዘመናዊ የመዝናኛ ሥርዓቶች የተካተቱላቸው መሆናቸውን ጠቁሟል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version