ኤስካይ 2 አዲስ ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖችን ተረከበ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኤስካይ (አፍሪካን ስካይ) ሁለት አዲስ ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖች መረከቡ ተገለጸ፡፡
አዲሶቹ የቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላኖች የነዳጅ ፍጆታ መቀነስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ያላቸው መሆናቸውንም የኤስካይ 40 በመቶ ድርሻ ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያወጣው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላኖቹ የውስጥ ክፍል÷ ሰፊ እና ዘመናዊ ከመሆናቸው ባሻገር÷ የተሻሻሉ የመቀመጫ አማራጮች ያላቸው እንዲሁም መንገደኞች በበረራ ወቅት እየተዝናኑ እንዲጓዙ የሚያስችሉ ዘመናዊ የመዝናኛ ሥርዓቶች የተካተቱላቸው መሆናቸውን ጠቁሟል።