Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የመስዋዕትነት ቀን በአፋር ክልል እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጳጉሜን 2 የመስዋዕትነት ቀን በአፋር ክልል በተለያዩ መርሐ ግብሮች እየተከበረ ነው፡፡

ቀኑ “በመስዋዕትነት የምትጸና ሀገር” በሚል መሪ ሃሳብ ነው በተለያዩ ዝግጅቶች በሰመራ ከተማ እየተከበረ የሚገኘው፡፡

በመርሐ ግብሩ የሕይወት መስዕትነት ለከፈሉ የሀገር መከላከያ የሰራዊት አባላት፣ ለአፋር ክልል ፖሊስ እና ለሌሎች ጸጥታ አካላት እውቅና ተሰጥቷል፡፡

Exit mobile version